የእግዚአብሔር ፍቅር እና ፍትሕ
1ኛ ሩብ ዓመት 2025
1 ዮሐ. 4:8 እና 16 እግዚአብሔር ፍቅር ነው ይላል። መላው መጽሐፍ ቅዱስ ይህን እውነታ ይመሰክራል። የክርስትና እምነት ማዕከሉ የእግዚአብሔር ፍቅር ነው። ፍቅር የእግዚአብሔር ማንነት እምብርት ነው፤ እኛም የምናምነውና የምንሰራው ነገር ሁሉ ማዕከል ፍቅር መሆን አለበት። በዚህ መሠረት ፍቅርን የምንረዳበት መንገድ በእምነታችን እና በድርጊታችን ላይ ተፅዕኖ ይኖረዋል።